አስደሳች ዜና  ወጋገን ባንክ በሽረ ዲስትሪክት ቅርንጫፎቹ ዳግም አገልግሎት መስጠት ጀመረ

አስደሳች ዜና ወጋገን ባንክ በሽረ ዲስትሪክት ቅርንጫፎቹ ዳግም አገልግሎት መስጠት ጀመረ

ተቋርጦባቸው በቆዩት በሽረ ዲስትሪክት ስር በሚገኙት፡- ሽረ፣ እንዳስላሴ ፣ምድረ ገነት፣ ዕዳጋ ሽረ፣ ስሁል ሽረ እና ምድረ ሓየሎም ቅርንጫፎቹ ዳግም አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ለክቡራን ደንበኞቹ ሲገልፅ ከፍተኛ ደስታ ይሰማዋል፡፡ ባንካችን ከሳምንት በፊት በአላማጣና በራያ ጥሙጋ ቅርንጫፎች አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ይታወሳል፡፡
እንዲሁም ሰቲት ሁመራ፣ አዲ ረመፅ ፣ ዳንሻ እና ተከዜ ቅርንጫፎች ቀደም ብለው ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ለማስታወስ እንወዳለን በቅርቡም አስፈላጊ ሁኔታዎች እንደተመቻቹ በተቻለ ፍጥነት ቀሪ ቅርንጫፎቻችንን በመክፈት አገልግሎታችንን ለሁሉም ህብረተሰብ የምናዳርስ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን፡፡

About the Author

Comments are closed.