ለውድ የወጋገን ባንክ የሸዋ ግብይት ካርድ ተጠቃሚ ደንበኞች
ወጋገን ባንክ አ.ማ እና ሸዋ ሾፒንግ ሴንተር በአብሮነት ሲሰጥ የነበረውን የቅድመ ክፍያ እና የስጦታ ካርድ ግብይት አገልግሎት በተሻለ መልኩ ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን፤ ለዚህም ይረዳ ዘንድ ቀደም ሲል ለደንበኞች ታድለው የነበሩ የሸዋ ግብይት ካርዶችን ጥቅም ላይ በማዋል ያለው ቀሪ ሂሳብ እንዲጠናቀቅ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡በመሆኑም ቀሪ ሂሳብ ያለው የሸዋ ግብይት ካርድ በእጃችሁ የሚገኝ ክቡራን ደንበኞቻችን ከታህሳስ 23 እስከ ጥር 23 ቀን 2016 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ 30 ቀናት በዘፍመሽ፣ ሳርቤት እና ሰሚት የሸዋ ሾፒንግ ሴንተር ቅርንጫፎች ግብይት በመፈፀም ያላችሁን ቀሪ ሂሳብ እንድታጠናቅቁ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
በሞባይል ቁጥር የተመዘገቡ
ያልተመዘገቡ